Friday, 22 January 2016

ይድረስ ለጎንደር ሕዝብ፣ ወያኔን ማመን፤ ውሃን እንድመጨበጥ ነው! (የጎንደር ሕብረት)


የጎንደር ሕብረት ዛሬም እንደ አለፉት መግለጫዎቻችን፤ በጎንደር ህዝብ ላይ የሚፈጽመውን የግፍ ተግባሮች አደባባይ በማውጣት፤ አገር አድን ብሔራዊ ትግላችንን የምናጠናክርበትን ስልት የማጠናከሩን ዓላማ ግብ ለማድረስ ነው። ይህ ሲባል ግን፤ በጦርነት ተወልዶ፤ በጦርነት እያረጀ ያለው፤ አገር አጥፊው የወያኔ ቡድን፤ በወረቀት ብቻ ይወድቃል ብለን ማመናችን አይደለም። መግለጫ፤ ጠላትን ያጋልጣል። ባንፃሩም ወገንን ያሥተባብራል፤ ያደራጃል፤ ያሥታጥቃል፤ በመጨረሻም ጠላቱን ይደመሥሳል።gonder-unity
ባለፉት 25 ዓመታት የጎንደር ሕዝብ የተፈጸመበትን ሰቆቃና ግፍ ለመዘርዘር በየጊዜው በምናወጣቸው ጥቂት ገጾች ላይ ብቻ ተዘርዝሮ የሚያበቃ ሳይሆን ሙሉ መጽሐፍ እንኳ አይበቃውም። ወያኔዎች ዛሬም እንደ ትናንቱ በሕዝባችን ላይ አረመኒያዊ ጭፍጫፋ ለማካሄድ ኃይላቸዉን አጠናክረዉ ወደ መተማና ቋራ የግዛት መረባቸውን ለመዘርጋት ልዩ ቅልብ ጦር አሰማርተዋል ። ይህ ቅልብ ሰራዊት በወያኔ ካድሬነት ለፖለቲካ ተግባር ተሰማርቶ የሁለቱን ማህበረሰብ ለማጋጨጥ ለቅማንት ወገኖቻችን ከናንተ ጋር ነን አይዟችሁ ሲሉ፤ ለአማራዉ ማህበረሰብ ደግሞ ከናንተ ጎን ሁነን ቅማንትን ድራሹን እናጠፋለን እንደሚሉ ከመሬት ላይ በነጋዴ ባህር፤ በዳንጉራ እና በዳዋ የተረጋገጠ መረጃ ደርሶናል። ይህ አገርን ለማጥፋት ትዉልድን በጥላቻ የመበከል በሽታን እያጋብን ያለን መሰሪ ኃይል፤ የዘር ጎራ ሳንለይ በህብረት ጠንክረን መዋጋት እና ራሳችንን ነፃ ማውጣት፤ ታሪካዊ እና አገራዎ ግዴታችን ነው።                                                                                   ምንጭ ECADF news

No comments:

Post a Comment