ታሪክ በብሄረተኝነት መነጽር
*********************************************************
በተደጋጋሚ ከፋም ለማም የአማራ ታሪክ የአማራ ነው፤ ከሁለቱም በኩል ትምህርት ብቻ ነው መውሰድ ያለብን እያልን ለማስገንዘብ ስንሞክር ቆይተናል፡፡ አንድ ነገር በግድ መታወቅ አለበት፡፡ ታሪክን ለመናቆሪያነት መጠቀም ካሰብን ዘለአለም ስንጨቃጨቅ መኖር እንችላለን፡፡ ማለትም ላለመስማማት ከፈለግን መቸም አንስማማም፡፡ ይህም የሚሆነው በሶስት ምክንያቶች ነው፡፡ አንደኛ ያለፈውን ታሪክ ሙሉ ስእል ማግኘት ስለማንችል እና የምንመረኮዝባቸው ሀቆች በሙሉ ሊደርሱን ስለማይችሉ፡፡ ሁለተኛ የአለፈን ጊዜ በአሁን ጊዜ መመንዘርና መፍረድ በአመዛኙ ስህተት በመሆኑ እና ብዙዎቻችን ለዚህ ሰለባ ስለምንሆን፡፡ ሶስተኛ በታሪክ ውስጥ ሆነ ተብሎም ይሁን ሳይተሳብበት የተሰሩ ስህተቶች የግድ አይቀሬ ስለሆኑ፤ ማለትም ታሪክን የሚሰሩት የሰው ልጆች በመሆናቸው ሰውን የሚያጋጥመው ውስንነትና ስህተት ታሪክ ላይም የግድ ስለሚንጸባረቅ፡፡ ስለሆነም ስለታሪክ ስንነጋር እነዚህን ነገሮች በቅድሚያ ግምት ውስጥ ማስገባት ይጠበቅብናል፡፡ ይህም የአማራን ታሪክ እና አሁን ከጀመርነው የብሄረተኝነት እንቅስቃሴ ጋር አዋህደን ለማራመድ ይጠቅመናል፡፡ ይህ ጽሁፍ በአመዛኙ ሰሞኑን ፌቡ ላይ ሲንሸራሸሩ ለነበሩ ሚዛናዊ ያልሆኑ እይታዎች እንደመልስነት የታሰበ ነው፡፡
*********************************************************
በተደጋጋሚ ከፋም ለማም የአማራ ታሪክ የአማራ ነው፤ ከሁለቱም በኩል ትምህርት ብቻ ነው መውሰድ ያለብን እያልን ለማስገንዘብ ስንሞክር ቆይተናል፡፡ አንድ ነገር በግድ መታወቅ አለበት፡፡ ታሪክን ለመናቆሪያነት መጠቀም ካሰብን ዘለአለም ስንጨቃጨቅ መኖር እንችላለን፡፡ ማለትም ላለመስማማት ከፈለግን መቸም አንስማማም፡፡ ይህም የሚሆነው በሶስት ምክንያቶች ነው፡፡ አንደኛ ያለፈውን ታሪክ ሙሉ ስእል ማግኘት ስለማንችል እና የምንመረኮዝባቸው ሀቆች በሙሉ ሊደርሱን ስለማይችሉ፡፡ ሁለተኛ የአለፈን ጊዜ በአሁን ጊዜ መመንዘርና መፍረድ በአመዛኙ ስህተት በመሆኑ እና ብዙዎቻችን ለዚህ ሰለባ ስለምንሆን፡፡ ሶስተኛ በታሪክ ውስጥ ሆነ ተብሎም ይሁን ሳይተሳብበት የተሰሩ ስህተቶች የግድ አይቀሬ ስለሆኑ፤ ማለትም ታሪክን የሚሰሩት የሰው ልጆች በመሆናቸው ሰውን የሚያጋጥመው ውስንነትና ስህተት ታሪክ ላይም የግድ ስለሚንጸባረቅ፡፡ ስለሆነም ስለታሪክ ስንነጋር እነዚህን ነገሮች በቅድሚያ ግምት ውስጥ ማስገባት ይጠበቅብናል፡፡ ይህም የአማራን ታሪክ እና አሁን ከጀመርነው የብሄረተኝነት እንቅስቃሴ ጋር አዋህደን ለማራመድ ይጠቅመናል፡፡ ይህ ጽሁፍ በአመዛኙ ሰሞኑን ፌቡ ላይ ሲንሸራሸሩ ለነበሩ ሚዛናዊ ያልሆኑ እይታዎች እንደመልስነት የታሰበ ነው፡፡
ከዚህ በፊት የአማራ ብሄረተኝነት መስመር (1) ላይ የአማራ ማንነት ተገልጹዋል፡፡ የአማራ ታሪክ ተዋናዮች የሆነው ህዝብ በተለይም በታሪክ ላይ ሰፍረው የሚገኙት መሪዎችም ማንነታቸው ከዚሁ ከተጠቀሰው ሳይንሳዊ እሳቤ የሚወጡ አይደሉም፡፡ የአማራን ማንነት በቅጡ ካለመረዳታችን የተነሳ ይሄ ንጉስ አማራ አይደለም፤ ያ ንጉስ እትን ነው እያልን የራሳችንን ታሪክ ስንሸረሽር እንታያለን፡፡ መጀመሪያ አንድን ንጉስ ወይም ገዥ አማራ ነው ወይስ አይደለም ከማለታችን በፊት ስለአማራ ማንነት በጥቂቱም ቢሆን ማወቅ አለብን፡፡ የብሄረተኝነት እንቅስቃሴን እደግፋለሁ ወይም ቅርጽ እሰጠዋለሁ የሚል ሰው በመጠኑም ቢሆን ስለማንነት እንቅስቃሴዎችና መሰረቶች ማወቅ አለበት፡፡ ብሄረተኝነትን ለመቅረጽ መጀመሪያ ራስን ሰፋ አድርጎ መቅረጽ ያስፈልጋል፡፡ ይህ የተባለበት ምክንያት የብዙዎቹ ሰዎች ጽሁፎች ስህተት ወይም እውነት ናቸው ለማለት ሳይሆን የምንናገረው እውነትስ ሆነ ስህተት የተያያዝነውን የማንነት ፖለቲካ እንዴት ባለ መንገድ እና ሁኔታ እንደሚጠቅመው እና እንደሚጎዳው በደምብ እንዲታሰብበት ለማመላከት ነው፡፡
የብሄረተኝነት እንቅስቃሴ የወደፊት እቅድን የሚቀርጽ ሂደት ስለሆነ የወደፊቱን ለመቅረጽ የኋላ መነሻ ያስፈልገዋል፡፡ ብሄረተኝነት እንቅስቃሴዎች እንኳን ያለውን ታሪክ የሌለ አዲስ ነገር ይፈጥራሉ፡፡ የሰውን ቀልብ ማሰባሰብ እና ለአንድ አላማ አሰልፎ ግብን መጨበጥ የሚቻለው በሆነ አንኳር ወይም በሆኑ አንኳር ታሪካዊ ክስተቶች ዙሪያ ነው፡፡ ታሪክ በብሄረተኝነት እንቅስቀሴ ውስጥ እንደንብ አውራ (ንግስት) ነው፡፡ አውራው ወይም ንግስቲቷ የሌለችበት ንብ ይበተናል፡፡ ምክንያቱም አብሮ የሚያኖር ምክንያት ስለሌለው፡፡ እንደዚሁም የብሄረተኝነት እንቅስቃሴ አንድ ላይ አያይዞ ለአንድ ግብ የሚያሰልፍ ታሪክ ያስፈልገዋል፡፡ ከዚሁም በላይ የተጋጋለ ብሄረተኝነት ለማካሄድ የህዝቡን ያለፈ ታላቅነት መንገር የግድ ያስፈልጋል፡፡ ዛሬ ያለበት ቦታ ላይ ሊወድቅ እንደማይገባው ደጋግሞ መንገር እና ያለፈው ትልቅነቱ እንዲናፍቀው ማድረግ ያሻል፡፡ ብሄረተኝነት የዛሬው ያለንበት ሁኔታ ውድቀት ነው ብሎ ነው የሚነሳው፡፡ ወደፊት ታላቅ ለመሆን መጀመሪያ ከታላቅነት መውደቅን ማመን ያስፈልጋል፡፡
ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴን የሚወድ የእንትን ጠላት ነው ብለው የሚጽፉ ውስን ሰዎች አሉ፡፡ እንደአስተያየት ይከበርላቸዋል፡፡ ግን ነገርየው የማይጠቅም እና የእይታ ችግርን የሚያመለክት ነው፡፡ ንጉሱ እገሌን ግዛት በድለዋል ብሎ የሚያስብ ሰው እንደዛ ቢያስብ አይገርምም፡፡ በደል ከተባለ እንግዲህ ንጉሱ ላይ ሁሉም የሚነቅፍባቸው ይኖራል፡፡ እንግዲህ ዝም ተብሎ ሲታይ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ብቻ ሳይሆኑ ሌሎችም ነገስታት የሚጠቀስ ጉድለት ይኖርባቸዋል፡፡ እነዛን ጉድለቶች ወይም አሉ የተባሉ ጉድለቶች ጠምዝዞ ለራስ አላማ ማዋል ግን ስህተት ነው፡፡ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴን የሚወድ የእንትን ጠላት ነው የሚለው ሀሳብ ግን እንደቀላል መታየት የሌለበት ነው፡፡ አንድ ሰው የአማራ ብሄረተኝነትን እደግፋለሁ ብሎ ሲያበቃ እንደገና ራሱን ከመላው አማራ ነጥሎ የተወሰነ አካባቢ ጠበቃ ካደረገ ጨዋታ ፈረሰ ማለት ነው፡፡ አንድ የአማራ ብሄረተኛ ስለራሱ ትውልድ ቦታ ብቻ የተለየ ስሜት ካለው እና ያንኑ ስሜቱን ሌሎቹም እንዲጋሩለት ከጠየቀ ይህ ሰው ትክክለኛ የአማራ ብሄረተኛ ነው ማለት አይቻልም፡፡ የሆነ አካባቢ ሰው ስለሆንኩ ብቻ ለአካባቢየ የተለየ ስሜት የሚሰማኝ ከሆነማ ሙሉ ኪሳራ ውስጥ ወደቅኩ ማለት ነው፡፡ አንድ የአማራ ብሄረተኛ የትም ይወለድ የትም አጀንዳው የግድ መላው አማራ ነው መሆን ያለበት፡፡ በአራቱ ግዛቶች፤ በሌላው ኢትዮጵያ እና በተቀረው አለም ተበትኖ የሚገኝ አማራ ሁሉ የእየለት ህይወቱ ሊያሳስበን እና በፍጹም አንድ እይታ ልንመለከተው ይገባል፡፡ አማራ ነኝ ስል የወሎም ሆነ የጎጃም ወይ የሸዋ አልያም የጎንደር ወይም በመላው አለም የተበተነው አማራ ህመም በእኩል ይሰማኛል ማለቴ ነው፡፡ በአማራ ብሄረተኝነት ውስጥ ሌላ ጭብጦ ይዞ መገኘት የብሄረተኝነቱ ነገር ያልገባው መሆንን ያመለክታል፡፡ በነገራችን ላይ እንዲህ አይነት ክፍለ ሀገራዊ ስሜት ራሳቸውን ከየትኛውም ክፍለ ሀገር ጋር ማያያዝ የማይችሉትን የተበተኑ አማሮች ያገላል፡፡ ታዲያ አንዱን አማራ የበለጠ እያሰብኩለት ሌላውን ሆነ ብየ ከረሳሁት ምን ዋጋ አለው!
እንዲህ አይነት የአማራን ብሄረተኝነት ለራስ ትውልድ ቦታ እንዲያጎበድድ መጣር በንኡስ ብሄረተኝነት እንጅ በአማራ ብሄረተኝነት መነጽር ሊታይ የማይገባው ነው፡፡ አመክንዮው ራሱ የሚገርም ነው እኮ፡፡ ቀኃሥን መውደድ በምንም መንገድ ከአንድ አካባቢ ጠላትነት ጋር አይያዝም፡፡ አንድ ሰው ስለየትኛውም አካባቢ ችግር ምንም ሳያውቅ ንጉሱን ሊወድ ይችላል፡፡ ያ ማለት ሳያውቅ እንኳ በጠላትነት ሊያዝ ነው ማለት ነው፡፡ እንደዛማ ከሆነ በየቤቱ የቀኃሥ ፎቶ የሌለው የለም እና ንጉሱን እጅግ ብዙ አማራ ይወዳልና ንጉሱን መጥላት ስለማይቻል የአማራ ብሄረተኝነት ከነአካቴው መቅረት አለበት ማለት ሊሆን ነው እኮ፡፡ በነገራችን ላይ እንዲህ አይነት ንኡስ ብሄረተኛነት ሌላ ንኡስ ብሄረተኝነትን ሊፈጥር እንደሚችል መገንዘብ ያስፈልጋል፡፡ እጅግ አጥብቄ የእኔ መንደር ባልኩ ቁጥር ሌላ የእኔስ መንደር የሚል ቡድን እየፈጠርኩ መሆኔን መረዳት ይገበኛል፡፡ በዛ ላይ ንጉሱ በጎም ሆኑ አልሆኑ ንጉሱ ላይ እጣት ከመቀሰር በፊት ንጉሱን እንዲህ ብል የእርሳቸው ደጋፊ ሊርቀኝ ይችላል፤ ብሄረተኝነቱም ሊጎዳ ይችላል ብሎ ማሰብም ያስፈልጋል፡፡
እንዲህ አይነቱ ንኡስ ብሄረተኝነት ጎጅ ነው፡፡ ምክንያቱም የብሄረተኝነት ዋና አላማው በማናቸውም ሰበብ ህዝቡን አንድ ላይ ማሰባሰብ እና አንድ አይነት ስሜት እንዲኖረው ማድረግ ነው፡፡ እንዲህ አይነት የንኡስ ብሄረተኝነት አዝማሚያ ግን ህዝብን በአንድነት እንዳይቆም የመጋፋት አይነት ነገር ነው፡፡ በዛ ላይ ታሪክን ለመናቆሪያ መጠቀም የብሄረተኝነት ሌላው ተቃራኒ ጫፍ እንጅ ደጋፊ አይደለም፡፡ ከታሪክ ልንወስድ የሚገባው አንድነትን የሚያጎለብቱ እና የሚጠቅሙንን ብቻ ነው፡፡ ሌላውን በትምህርትነቱ እንይዘዋለን፡፡
ታሪክን በተመለከተ የአማራ ብሄረተኝነት በእውነት ላይ ብቻ መመስረት አለበት የሚለው አስተሳሰብ ስህተት ነው፡፡ በእርግጥ ብሄረተኝነት በእውነት ላይ ነው የሚገነባው፡፡ ያ ማለት ግን ብሄረተኝነት እንቅስቃሴ ፖለቲካ መሆኑን መርሳትን አያመለክትም፡፡ እውነት ብቻውን ፖለቲካዊ እቅስቃሴ ሊፈጥር አይችልም፡፡ እኛ የተያያዝነው የፍልስፍና ወይም የስነመለኮት ወይም የአካዳሚያዊ ታሪክ ትምህርት ክፍለጊዜን ማስፈን አይደለም፡፡ የአማራ ብሄረተኝነት ዋና አላማ ህዝብን በተገቢው ታሪካዊ ሀቆች ላይ በመመርኮዝ ለአንድ እጣ ፋንታ ማሰለፍ ነው፡፡ ታሪካዊ ጸጉር ስንጠቃውን ህዝባችን ነጻ ከወጣ በኋላ በመደበኛ የታሪክ ትምህርት ክፍለጊዜ እናስተምራለን፡፡ እውነትም ራሱ አንጻራዊ ነው እኮ፡፡ ቅንጭብ እውነት ይዘን የእውነት መጨረሻ ላይ የደረስንም ሊመስለን ይችላል፡፡ እውነትን ይዘን እንከራከር ብንል እንኳ እውነት በየደረስንበት የግንዛቤ ደረጃ ይወሰናልና እና ቋሚ መለኪያ አናገኝም፡፡ አንዱ እውነት ብሎ የያዘውን ሌላው በተጨማሪ እና ጥልቅ መረጃ ሊያፈርሰው ይችላል፡፡ ያም አለ ይህ የብሄረተኝነት አላማ እውነትና ሀሰት በሚል መነታረክ ሳይሆን ህዝብን በአንድነት ለተመሳሳይ አላማ ማቆም ነው፡፡ አማራ ህዝብ ትግል የህልውና መሆኑም መዘንጋት የለበትም፡፡
በአማራ ብሄረተኝነት ውስጥ የሞዐ አንበሣ አስተሳሰብ አያስፈልግም የሚል ደከም ያለ ነገርም ተጽፎ አይተናል፡፡ ቀኃሥን እንደሞዐ አንበሣ አድርጎ የማቅረብ ነገር ነው፡፡ ይን እንጅ ይህ የመረጃ እጥረት ነው፡፡ ቀኃሥ የሶሎሞናዊያን ስርዎ መንግሥት 225ኛ ንጉስ እንጅ ብቸኛ ንጉስ አይደለም፡፡ የሶሎሞናዊያን ስርወ መንግሥት ዋና አርማ ደግሞ ሞአ አንበሣ ነው፡፡ ስለዚህ ሞዓ አንበሳ በአርማነቱ የታሪካችን አካል እንጅ የአንድ ንጉስ ብቻ አሻራ አይደለም፡፡ ይሄንን ደግሞ መፋቅ አይቻልም፡፡
ቀዳማዊ አጼ ኃይለ ሥላሴ የአማራ ጠላት ናቸው፡ አማራን ለማጥፋት ሰርተዋል የሚሉ ክሶችም ታይተዋል፡፡ እንግዲህ ቀኃሥ የአማራ ጠላት ናቸው፤ አማራን ሲያጠፉ ነው የኖሩ የሚለው ውንጀላ መሰረተ ቢስ ነው፡፡ እሳቸው እንደ አንድ የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግስታዊ ሀላፊነቶችን ለሁሊም አካባቢ ለማዳረስ እና አገሪቷን ህዝቡ በአንድ ጥላነት እንዲቀበላት ጥረዋል፡፡ በተለየ ሁኔታ አማራን አጠፉ የሚለው አጉል ክስ ነው፡፡ በእርግጥ ተቀናቃኞቻቸውን አጥፍተዋል፡፡ ያ ደግሞ የፖለቲካው ባህርይ እንጅ የንጉሱ የተለየ አማራን የማጥፋት ፖሊሲ ተደርጎ ሊወሰድ አይገባም፡፡ ደግሞም አማራን አጠፉ የሚለውን ቃል ለእኝ ንጉስ መስጠት ጨካኝነት ነው፡፡ የተወሰኑ ተቀናቃኞችን ማፈናቸው ወይም ማጥፋታቸው አማራን ማጥፋት ተደርጎ ሊወሰድ አይችልም፡፡ በእርግጥ ስልጣናቸውን ለማማከል ወይም አሀዳዊ አገርን ለመፍጠር የየአውራጃና ጠቅላይ ግዛት ሹሞችን ሀይል አሳጥተው ማእከላዊ ጦር መስርተዋል፡፡ ይህ ሂደት እርሳቸው ያደረጉት ብቻ ሳይሆን ጣልያን በትልቁ አሻራውን ያሳረፈበት ነው፡፡ የየግዛት ሀይል ተዳክሞ በአንድ ማእከላዊ እዝ ስር የመውደቁ ሁኔታ ደግሞ የዘመኑ ሁኔታ ውጤት እንጅ የንጉሱ ብቻ መለኮት- መራሽ ስራ ውጤት አይደለም፡፡ እርሳቸውም እዛ ቦታ ላይ ባይሆኑ ሌላው ሊያደርገው የሚችለው ወይም በራሱ ጊዜ የሚሆን ክስተት ነው፡፡ የ1953ቱ መፈንቅለ መንግሥት ሙከራ ሙሉ በሙሉ ሊባል በሚችል ሁኔታ በአማሮች የተከናወነ ነው፡፡ ያ ማለት ደግሞ ስልጣን ላይ አማሮች ነበሩ ማለት ነው፡፡ እንደጉድለት ከተቆጠረ ንጉሱ መኳንንትን ችላ በማለት ከተራው ህዝብ ወገን የሆኑ ሰዎችን ለወግ ለማእረግ አብቅተዋል፡፡ ግን አማራን ሆነ ብለው በደሉ የሚለው አያስኬድም፡፡
በመጨረሻም ነገስታቶቻችንን ከአማራ መነጠል ምን ጉዳት ያመጣል የሚለውን በቀጣይ የአማራ ብሄረተኝነት መስመር (3) እንመለስበታለን፡፡
መለክ ሐራ
No comments:
Post a Comment